ሕይወት ተረፉ በቀለ (እሙ) ታላቅ ተነሳሽነትን ያታደለ ልብ ባለቤት እና የቦስተን ከተማ ነዋሪ ናት። በቦስተን ውስጥ ከሚገኘውና ከተለያዩ የማህበረሰብ ክፍል የመጡ ሰዎች ተሰባስበው ከሚኖሩበት እና ብዙ ዓይነት ባህልና ልማዶች ውህድ ውበት ተጣምሮ ከሚታይበት ኬምብሪጅ ከተማ የመንግስት ትምህርት ቤቶች ክፍል በአንዱ ውስጥ ለምትወደው ማህበረሰብ ጊዜዋን በመስጠት ትሰራለች። ለቤተሰቦቿ የመጨረሻ ሴት ልጅ ከመሆኗም በላይ፤ ለወንድምና ለእህቶችዋ ምርጥ እህት፣ ተወዳጅ አክስት፣ ጨዋታ የምትወድ ክርስትና እናት እና መልካም ጓደኛም ናት። ሕይወት ከኢትዮጵያዊ አሜሪካዊነቷ ከወረሰችው ማንነቷ እና ከምስራቅ አፍሪካዊነቷ ባህል ጋር ባላት የጠበቀ ቁርኝት ምክንያት ለቤተሰብ፣ ጓደኝነት እና ማህበረሰብ ላለው የአብሮነት ኃይል ዋጋ ትሰጣለች። የሕይወት የስነፅሁፍ ፍላጎት የጀመረው ገና የመጀመሪያ ትምህርት ቤት ተማሪ ሆና ሲሆን፤ የስነፅሁፍ ችሎታዋ የተለያዩ ሽልማቶች ባለቤት እንድትሆን አድርጓታል። ለሰብዓዊ መብቶች መከበርና በልዩነቶች ላይ ተከባብሮ ስለመኖር ያላትን አቋም በግልጽነት በመናገርዋና ስለተግባራዊነቱም ባደረችው ተሳትፎ ለኮሌጇ ልዩ የሰብዓዊነት ሽልማት ተሸላሚነት አብቅቷታል። ከዚህም በተጨማሪ በኮሌጇ በሚታተመው የስነፅሁፍ መጽሄት ላይም ግጥሟ መታተም ችሏል። ያሳደጋት ማህበረሰብ የካበተ ባህልና ወግ በቀረጸባት አመለካከት እና ለህብረተሰቡ ያላት የፍቅር መሰረት እሙ ልጆች ለቤተሰብ፣ ለማህበረሰብ ብሎም ለዓለም ታላቅ ስጦታ መሆናቸውን እንድታምን አድርጓታል። እናም ልጆች ፍቅርን ተመግበው እንዲያድጉ፣ ክፉ ነገር እንዳይደርስባቸው እና ወደ መልካም መንገድ እንዲያመሩ ለማስቻል ትተጋለች። ለዚህም ለጊዜው አንድ ታሪክ በቂ ነው ትላለች